ለተፈናቃዮች ከ8 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት የአይነት ድጋፍ ተደረገ
በገቢዎች ሚኒስቴር የከፍተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ከሰራተኞቹና ከአመራሩ እንዲሁም ከድርጅቶች ያሰባሰበውን ከ5 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመቱ ምግብ፣ አልባሳት፣ የንጽህና መጠበቂያ እና ልዩ ልዩ ቁሳቁሶችን በጦርነት ምክንያት ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው ሸዋሮቢት ከተማ ለሚገኙ ወገኖች ድጋፍ ማድረጉ ተገልጿል፡፡
የቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቱ ስራ አስኪያጅ አቶ ተሬሳ ኢንሱስ፥ ድጋፉ ካለው ተፈናቃይ ቁጥር አንጻር በቂ ባይሆንም በተወሰነ ደረጃ እንደሚያግዝ ገልጸው ድጋፉ ቅድሚያ ለሚያስፈልጋቸው ቅድሚያ በመስጠት በፍትሃዊነት ለተፈናቃዮች እንዲደርስ አስተባባሪዎች ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ጠይቀዋል፡፡
ነዋሪዎቹ ተረጋግተው ወደመደበኛ የዕለት ተዕለት ተግባራቸው እስኪመለሱ ድረስም ድጋፍን በቀጣይም አጠናክሮ እንደሚቀጥል መናገራቸውን ከገቢዎች ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
ድጋፉን የተረከቡት የከተማው አፈጉባኤ አቶ ግርማ ኃይሉ ለተደረገው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል፡፡
አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!