የተለያዩ ክልል ከፍተኛ አመራሮች በወቅታዊ አገራዊና ክልላዊ ጉዳዮች ላይ እየመከሩ ነው
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ከፍተኛ አመራሮች በወቅታዊ አገራዊና ክልላዊ ጉዳዮች ዙሪያ በቦንጋ ከተማ እየመከሩ ይገኛሉ።
ዛሬ በተጀመረው የውይይት መድረክ የክልሉ ካቢኔ አባላት፣ ሌሎች ከፍተኛ አመራሮችና የዞን አመራሮች እየተሳተፉ ነው።
በመድረኩ ዝርዝር አገራዊና ክልላዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት ተደርጎ ቀጣይ አቅጣጫዎች ይቀመጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በሌላ በኩል የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ ውይይት አካሄደዋል።
በውይይቱ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ፣ የክልሉ የብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አብርሃም ማርሻሎ፣ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ በየነ ባራሳ፣ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ ፋንታዬ ከበደ፣ የክልል ከፍተኛ አመራሮች፣ የወረዳና ከተማ አስተዳደሮች አመራሮች መሳተፋቸውን ከክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጽህፈት ቤትያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!