በአሜሪካ ፊኒክስ እና አሪዞና የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በአሸባሪው የህወሓት ቡድን ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች 120 ሺህ ዶላር አሰባሰቡ
አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 7 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአሜሪካ ፊኒክስ እና አሪዞና ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በአሸባሪው የህወሓት ቡድን ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ማቋቋሚያ ይውል ዘንድ 120 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ተሰበሰበ፡፡
በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ፍጹም አረጋ፥ በፊኒክስ እና በአሪዞና የሚኖሩ የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ አባላት እና ድጋፉን በማሰባሰብ ረገድ የመሪነት ሚና የተጫወቱትን አስተባባሪዎች አመስግንዋል።
አምባሳደሩ “እርስ በእርስ ስንረዳዳ ከፍ እንላለን” ሲሉ በማኅበራዊ ትስስር ገፃቸው መልዕክት አስተላልፈዋል።