Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያ ከፓኪስታን ጋር ያላትን አጋርነት ለማጠናከር ትሰራለች – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ ከፓኪስታን ጋር ያላትን አጋርነት ለማጠናከር በቁርጠኝነት ትሰራለች አሉ፡፡

የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ሸህባዝ ሸሪፍ ብልጽግና ፓርቲ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በማሸነፉ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ያስተላለፉት መልዕክት የሁለቱን ሀገራት የእህትማማችነት መንፈስ የሚያንጸባርቅ መሆኑን ጠቅሰው፥ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

ኢትዮጵያ እና ፓኪስታን በእድገት ጎዳና ላይ እንደሚገኙ ገልጸው፥ ሁሉን አቀፍ እድገትን እውን ለማድረግ በጋራ መቆማቸውን አንስተዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.