Fana: At a Speed of Life!

የጉጂን ዞን ሠላም የሚያደፈርሱ የሸኔ አባላት በሠላም ኅብረተሰቡን እንዲቀላቀሉ አባገዳዎች ዳግም ጥሪ አቀረቡ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 19፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የጉጂን ዞን ሠላም የሚያደፈርሱ የአሸባሪው ሸኔ ቡድን አባላት በሠላም ኅብረተሰቡን እንዲቀላቀሉ የጉጂ አባ ገዳዎች ዳግም ጥሪ አቀረቡ፡፡

የጉጂ አባ ገዳዎች እንደገለጹት፥ የአሸባሪው ሸኔ አባላት በሠላም ወደ ኅብረተሰቡ እንዲቀላቀሉ ጥሪ የቀረበው ለመጨረሻ ጊዜ እንደሆነ እና የጥሪውም ዓላማ ለዞኑ ሠላም ቅድሚያ በመስጠት ልማት አጠናክሮ ለማስቀጠል እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡

የጉጂ ዞን ባሕልና ቱሪዝም ጽህፈት ቤት ኃላፊ አዶላ ሚኤሳ በበኩላቸው፥ የአባ ገዳዎቹ ጥሪ ለዞኑ ሠላም እና መረጋጋት ጉልህ ሚና እንዳለው ጠቁመው፥ የዞኑ ማኅበረሰብ ለሠላማዊ ጥሪው ሁኔታዎችን በማመቻቸት የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ መጠየቃቸውን የዘገበው ኦቢኤን ነው፡፡

አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.