ምርጫ ቦርድ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር እየተወያየ ነው
አዲስ አበባ፣ ጥር 18፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ በተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል የሚደረግ ውይይት በሚመራበት መመሪያ ላይ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር እየመከረ ነው፡፡
የውይይት መመሪያ ሰነዱ የፖለቲካ ፓርቲዎች እርስ በእርስ የሚያደርጉት ውይይት እንዴት መካሄድ እንዳለበት የሚወስን መሆኑ ተመላክቷል፡፡
ሰነዱ በፓርቲዎች ከፀደቀበት ጊዜ ጀምሮ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሚያደርጉት ውይይት እስከሚጠናቀቅበት ድረስ የጸና እንደሚሆን ነው የተገለጸው፡፡
አሁን ላይም በኢትዮጵያ ለግጭት ምክንያት ሆነዋል የሚባሉ ጉዳዮችንም ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች አጀንዳዎችን በማቅረብ ውይይት እየተደረገ ነው፡፡
በታሪኩ ለገሰ
ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!