Fana: At a Speed of Life!

መሀል ሜዳ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል አገልግሎት መሥጠት ጀመረ

አዲስ አበባ፣ ጥር 23፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአሸባሪውና ዘራፊው የህወሓት ቡድን ጉዳት ደርሶበት የሕክምና አገልግሎት ያቋረጠው የመሀል ሜዳ ሆስፒታል በተደረገለት ድጋፍ አገልግሎት መሥጠት ጀመረ፡፡

የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሉ ÷በዳግማዊ ምኒልክ ሆስፒታልና በአካባቢው ማኅበረሰብ በተደረገለት ድጋፍ የሕክምና አገልግሎት መሥጠት መጀመሩን የሆስፒታሉ ሥራ አስኪያጅ ወርቅነህ ዘዉዴ ተናግረዋል።

ሥራ አስኪያጁ ÷ሆስፒታሉ በተደረገለት የሕክምና መገልገያ መሳሪያዎችና የመድኃኒት አቅርቦት ድጋፍ የእናቶችና የሕፃናት ጤና አገልግሎት፣ የድንገተኛና ጽኑ ሕሙማን አገልግሎት እንዲሁም የተመላላሽ ሕክምና አገልግሎቶችን መሥጠት ጀምሯል፡፡

በየዕለቱ በአማካይ ከ 150 እስከ 200 ታካሚዎች አገልግሎት እያገኙ እንደሚገኝም ነው የተመለከተው፡፡

ሆስፒታሉ በሙሉ አቅሙ እንዲሠራ ተጨማሪ ድጋፎች እንደሚያስፈልጉም ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል።

በመሀል ሜዳ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የሚሠሩ የህክምና ባለሙያዎች ÷ የአምቡላንስ አገልግሎት በመስተጓጎሉ በእናቶችና በድንገተኛ ጤና አገልግሎት ላይ ተጽእኖ ማሳደሩን መግለጻቸውን የጤና ሚኒስቴር በመረጃው አመላክቷል::

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.