Fana: At a Speed of Life!

ኃይሌ ሆቴሎችና ሪዞርቶች በወልቂጤ ከተማ ለሚገነባው 11ኛ ቅርንጫፍ የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ

አዲስ አበባ፣ጥር 29፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ኃይሌ ሆቴሎችና ሪዞርቶች በወልቂጤ ከተማ ለሚገነባው 11ኛ ቅርንጫፍ የመሰረት ድንጋይ ዛሬ ተጥሏል፡፡
 
ሻለቃ አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ አስተዳደር በሆቴል ኢንቬስትመንት ለመሰማራት በተረከበው 5 ሺህ 352 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ግንባታ ለማስጀመር በደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ርስቱ ይርዳው በዛሬው ዕለት የመሰረት ድንጋይ ተቀምጧል፡፡
 
የሪዞርቱ ግንባታ በግማሽ ቢሊየን ብር እንደሚከናወን የገለፀው÷ ሻለቃ አትሌት ኃይሌ ግንባታውን በአጭር ጊዜ በመጀመር በፍጥነት ለማጠናቀቅ በትኩረት እንደሚሰራ ተናግሯል።
 
አትሌቱ በደቡብ ክልል ለሚያከናውናቸው የኢንቬስተመንት ስራዎች የክልሉ መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ርዕሰ መስተዳደሩ ርስቱ ይርዳው መናገራቸውን ደሬቴድ ዘገቧል።
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.