“በወጪ ምርት ዘርፍ በጣም ግዙፍ ዕመርታ ታይቷል ”- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 30፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለፉት ሁለት ዓመታት በወጪ ምርት ዘርፍ በጣም ግዙፍ ዕመርታ ታይቷል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ገለጹ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ በተካሄደው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስብሰባ ላይ የወጪ ምርት እድገትን በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያ÷ ባለፉት ሁለት ዓመታት በተሠራነው ሥራ በሸቀጦች የወጪ ምርት ከአራት ቢሊየን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን ገልጸዋል፡፡