ስሎቬኒያ በኢትዮጵያ ኤምባሲ ልትከፍት ነው
አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 3 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ስሎቬኒያ በኢትዮጵያ ኤምባሲ ልትከፍት መሆኑ ተገለጸ፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ ከስሎቬኒያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ልዩ መልዕክተኛ ሬናታ ቬልባር ጋር ተወያይተዋል።
በውይይታቸውም አምባሳደር ብርቱካን አያኖ ስሎቬኒያ ኤምባሲዋን በኢትዮጵያ እንድትከፍት አስፈላጊውን ትብብር ሁሉ እንደሚያደርጉ ማረጋገጣቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።