Fana: At a Speed of Life!

በ5ኛው ዙር የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ- ግብር 6 ነጥብ 3 ቢሊየን ችግኝ እንደሚተከል ግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 4፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)በሀገር አቀፍ ደረጃ በ5ኛው ዙር የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር 6 ነጥብ 3 ቢሊየን ችግኝ ለመትከል መታቀዱን ግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

ከሚተከለው ውስጥ 45 በመቶው ለደን የሚውል ሲሆን ቀሪው 55 በመቶ ደግሞ ለጥምር ግብርና እና ፍራፍሬ ልማት ይውላል ተብሏል፡፡

የዐረንጓዴ ዐሻራ መርሐ- ግብር ለአካባቢ ጥበቃ እና ለተፈጥሮ ሐብት ልማት መፍትሄ ከመሆን ባሻገር የምግብ ዋስትን ለማረጋገጥ ያግዛልም ነው የተባለው።

በአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ 1 ነጥብ 8 ሚሊየን ሄክታር መሬት ማዳረስ መቻሉም ተገልጿል።

ቀደም ሲል የአፈር መሸርሸርን ለመከላከል የተሠሩ ሥራዎች በአሁኑ ሰዓት ጥገና እንዳስፈለጋቸው እና በዚሁ መሠረት 1 ሚሊየን ሄክታር ያህሉ የመስኖ ልማት ሥራ ጥገናና ዕድሳት እንደተደረገለት ነው የተገለጸው።

ተዳፋት የሆኑና የተራቆቱ አካባቢዎችን ከንክኪ ነፃ በማድረግ መልሶ ለማልማት በተያዘው ዕቅድ 800 ሺሕ ሄክታር መሬት መሸፈን መቻሉም ተጠቁሟል፡፡

መርሐ-ግብሩ ሕዝብ አሳታፊ መሆኑም ተጠቁሞ ከ2 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ማኅበራት በባለቤትነት መሠጠቱ ተመልክቷል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.