Fana: At a Speed of Life!

ጠ/ ሚ ዐቢይ ከጀኔራል አብደል ፈታህ አልቡርሃን እና ከጀኔራል ሞሃመድ ሃምዳን ዳጋሎ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 20፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከሱዳን ጦር ዋና አዛዥ ጀኔራል አብደል ፈታህ አልቡርሃን እና ከሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሃይሎች ዋና አዛዥ ሞሃመድ ሃምዳን ዳጋሎ ጋር በስልክ ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም÷ሁለቱ መሪዎች ልዩነቶቻቸውን በመግባባት እንዲፈቱ እና ለሀገራቸው መረጋጋትን ማምጣት በሚችሉበት ሁኔታ ላይ መክረዋል።

ታላቁ የሱዳን ሕዝብ ሰላም ያስፈልገዋል ሲሉም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ አስፍረዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.