Fana: At a Speed of Life!

በአንድ ጀንበር 500 ሚሊየን ችግኝ የመትከል መርሐ ግብር ከማለዳ ጀምሮ እስከ 8፡30 ድረስ ከ372 ሚሊየን በላይ ችግኝ ተተክሏል

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 10፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በዛሬው ዕለት እየተካሄደ በሚገኘው በአንድ ጀንበር 500 ሚሊየን ችግኝ የመትከል መርሐ ግብር ከማለዳ ጀምሮ እስከ 8 ሰዓት ተኩል ድረስ 372 ሚሊየን በላይ ችግኝ መተከሉን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ገለጸ።

ከችግኝ ተከላ ሁነቶች መከታተያ ክፍል የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰላማዊት ካሳ በሰጡት መግለጫ እንደገለጹት÷ በመላ ሀገሪቱ 500 ሚሊየን ችግኝ በአንድ ጀንበር የመትከል መርሐ ግብር እንደቀጠለ ነው፡፡

በእያንዳንዱ የኢትዮጵያ ክፍል 12 ሰዓት እስከ 8 ሰዓት ተኩል ድረስም ከ372 ሚሊየን በላይ ችግኞች መተከላቸውን ተናግረዋል።

በመርሐ ግብሩ ህፃናት፣ ወጣቶች እና አረጋውያንን ጨምሮ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ችግኝ በመትከል ታሪክ እየሰራ ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡

በምንተስኖት ሙሉጌታ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.