የደሴ-ኮምቦልቻ-ከሚሴ-ደብረብርሐን አዲስ አበባ የየብስ ትራንስፖርት አገልግሎት ጀመረ
አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 8፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ለጊዜው ተቋርጦ የነበረው የደሴ-ኮምቦልቻ-ከሚሴ-ደብረብርሐን አዲስ አበባ የየብስ ትራንስፖርት አገልግሎት በዛሬው እለት ሙሉ በሙሉ አገልግሎት መስጠት መጀመሩ ተገለፀ።
በአንድአንድ የአማራ ክልል አካባቢዎች ሰሞኑን ተፈጥሮ በነበረው አለመረጋጋት በተጠቀሱት አካባቢዎች በተወሰነ መልኩ አገልግሎቱ ተቋርጦ እንደነበር ይታወሳል፡፡