Fana: At a Speed of Life!

የዓለም ባንክ ሥደተኞችን በተመለከተ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥል ተጠየቀ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 17፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም ባንክ ለሥደተኞች እና ሥደተኞችን ለሚያስተናግዱ ማኅበረሰቦች የሚያደርገውን ድጋፍ ይበልጥ እንዲያጠናክር የሥደተኞች እና ከሥደት ተመላሾች አገልግሎት ዳይሬክተር ጀነራል ጠይባ ሐሰን ጠየቁ፡፡

ዳይሬክተር ጀነራል ጠይባ ሐሰን ÷ በኢትዮጵያ የዓለም ባንክ ከፍተኛ ኦፊሰር ከሆኑት ሞሐመድ ከድር አብዴል-ራዚግ ጋር ተወያይተዋል፡፡

ባንኩ በድጋፍ በኩል እስካሁን ላበረከተው ከፍተኛ አስተዋፅዖም በመርሐ-ግብሩ ላይ ማመስገናቸው ተገልጿል፡፡

በቀጣይም አገልግሎቱ ይበልጥ የተሻለ ምላሽ ይሰጥ ዘንድ የዓለም ባንክ ድጋፉን እንዲያጠናክር ጠይቀዋል።

በኢትዮጵያ የዓለም ባንክ ከፍተኛ ኦፊሰር ሞሐመድ ከድር አብዴል-ራዚግ በበኩላቸው ÷ የዓለም ባንክ ከኢትዮጵያ መንግስት እንዲሁም ከሥደተኞች እና ከሥደት ተመላሾች አገልግሎት ጋር በትብብር መሥራቱን እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡

ኢትዮጵያ ሥደተኞችን በማስተናገድ ረገድ እየተወጣች ያለውን ሚና አድንቀው የዓለም ባንክ ድጋፉን አጠናክሮ ይቀጥላልም ብለዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.