Fana: At a Speed of Life!

የአፍሪካ ህብረት ጋቦንን ከአባልነት ተሳትፎ አገደ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 26፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፍሪካ ህብረት በጋቦን የተካሄደውን መፈንቅለ መንግስት ተከትሎ ሀገሪቷን ከአባልነት ተሳትፎ ማገዱን አስታወቀ፡፡

የጋቦን ወታደራዊ አመራሮች በተያዘው ሳምንት የመንግስትን ስልጣን መቆጣጠራቸውን ይፋ ማድረጋቸው ይታወሳል፡፡

የአፍሪካ ህብረት የሰላምና ፀጥታ ም/ቤት ጉዳዩን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ÷የጋቦን ጦር በሀገሪቱ ፕሬዚዳንት አሊ ቦንጎ ላይ ያደረገውን መፈንቅለ መንግስት አውግዟል፡፡

ፕሬዚዳንት አሊ ቦንጎ በ ሀገሪቱ በተካሄደው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ 64 ነጥብ 27 በመቶ ድምጽ በማግኘት ለ3ኛ የስልጣን ዘመን መመረጣቸው ይፋ ተደርጎ ነበር፡፡

ወታደራዊ መፈንቅለ መንግስቱን ተከትሎም የአፍሪካ ህብረት ጋቦንን ከየትኛውም የአባልነት ተሳትፎ ማገዱን አልጀዚራ ዘግቧል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.