Fana: At a Speed of Life!

አቶ ደስታ ሌዳሞ ከሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች ጋር እየተወያዩ ነው

 

አዲስ አበባ ፣ መስከረም 22፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በሀዋሳ ከተማ ልማትና መልካም አስተዳደር ስራዎች ዙሪያ ከከተማው ህብረተሰብ ክፍሎች ጋር እየተወያዩ ነው፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ በውይይቱ ወቅት÷ የክልሉ መንግስት የከተማው ህብረተሰብ ጥያቄዎችን ለመፍታት በቅርበት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።

የከተማው ህብረተሰብ ክፍል ቀድሞ በነበረው የከተማው አስተዳደር ላይ የክልሉ መንግስት የወሰደው የሪፎርም ስራ የሚበረታታ እንደሆነ የገለፁ ሲሆን÷ የነበረው የመልካም አስተዳደርና የልማት ስራዎች ክፍተት ሊታረም እንደሚገባ አሳስበዋል ነው የተባለው።

ርዕሰ መስተዳድሩ የከተማው ህብረተሰብ ክፍልን ሃሳብ ለመስማት ውይይቱን ማመቻቸቱን መናገራቸውን ከክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.