Fana: At a Speed of Life!

ከተማ አስተዳደሮች የባለሀብቱን ፍላጎት የሚያሟላ አገልግሎት መስጠት ይኖርባቸዋል ተባለ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 16፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአምራች ዘርፍ የተሰማሩ ባለሀብቶች የሚያነሱትን ጥያቄ ለመመለስ እንደሚሰራ የአማራ ክልል ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ አስታውቋል፡፡

የክልሉ ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ሀላፊ አሕመዲን (ዶ/ር) እና ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች በደብረ ብርሀን ከተማ በማምረትና ግንባታ ላይ ያሉ ኢንዱስትሪዎችን ጎብኝተዋል።

የክልሉ ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ሀላፊ አሕመዲን መሐመድ (ዶ/ር)÷ በክልሉ የተሰማሩ ባለሀብቶች የመሰረት ልማትና የማስፋፊያ መሬት ጥያቄዎች አሏቸው ብለዋል፡፡

እነዚህን ጥያቄዎች በፍጥነት በመፍታት ምቹ ሁኔታ እንፈጥራለን ሲሉም ገልጸዋል።

ሰላም ለኢንቨስትመንት ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው÷ የክልሉ መንግስት አሁን የተፈጠረውን አንጻራዊ ሰላም አስተማማኝ ለማድረግ እየሰራ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

የክልሉ ከተማ አስተዳደሮች የባለሀብቱን ፍላጎት የሚያሟላ አገልግሎት መስጠት ይኖርባቸዋል ያሉት ሀላፊው÷ የተንዛዛ ቢሮክራሲን ማስቀረት አለብን ሲሉ ገልጸዋል፡፡

በአላዩ ገረመው

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.