Fana: At a Speed of Life!

የጋዜጠኛ ዓይናለም ባልቻ ሥርዓተ-ቀብር ተፈጸመ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 15፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ለ25 ዓመታት ያገለገለችው ጋዜጠኛ ዓይናለም ባልቻ ሥርዓተ-ቀብር ዛሬ በቤተል ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ተፈጽሟል፡፡

ጋዜጠኛዋ በጣቢያው በልጆች ፕሮግራም ብቻ ለ15 ዓመታት ያገለገለች ሲሆን÷ በ55 ዓመቷም ትናንት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች፡፡

በጤና እክል ምክንያት ከሥራዋ ተገልላ በሕመም ላይ የነበረችው ጋዜጠኛ ዓይናለም÷ የአንዲት ሴት ልጅ እናት እና የሁለት የልጅ ልጆች አያት መሆኗ ይታወቃል፡፡

ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በጋዜጠኛ ዓይናለም ባልቻ ኅልፈት የተሰማውን ኀዘን እየገለጸ÷ ለቤተሰብ እና ወዳጅ ዘመድ መጽናናትን ይመኛል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.