Fana: At a Speed of Life!

ሁሉም ኢትዮጵያውያን በባህር በር ጉዳይ የበኩላቸውን አስተዋፅዖ ሊያደርጉ ይገባል ተባለ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ሁሉም ኢትዮጵያዊ ዜጋ ከፖለቲካ አመለካከት ልዩነት ወጥቶ በባህር በር ጉዳይ የበኩሉን አስተዋፅዖ ሊያደርግ እንደሚገባ የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር ኢ/ር) ተናገሩ፡፡

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት ከፍተኛ አመራሮችና ባለሙያዎች ኢትዮጵያ የባህር በር ለማግኘት የሚያስችላትን ስምምነት ከሶማሊላንድ ጋር መፈረሟን አስመልክቶ የተሰማቸውን ደስታ ገልፀዋል፡፡

በፕሮግራሙ የተገኙት ሚኒስትሩ፥ኢትዮጵያ በታሪኳ የባህር በርን በመጠቀም ከዓለም ማህበረሰብ ጋር የምታደርጋቸው የንግድና ሌሎች ግንኙነቶች እንደነበሩ አስታውሰዋል፡፡

በተለያየ ጊዜ ባጋጠሙ ፖለቲካዊ ችግሮች ኢትዮጵያ ከውሃ አካላት እንድትርቅ ተደርጓል ያሉት ሚኒስትሩ÷ አሁን ላይ ከሶማሌ ላንድ ጋር እጅግ ሰላማዊ በሆነ መንገድ እና ብስለት በተሞላበት የአመራር ጥበብ ወደ ባህር በር መጠጋታችን ትልቅ ኩራት ነው ብለዋል፡፡

በመሆኑም ማንኛውም ኢትዮጵዊ ከፖለቲካዊ አመለካከት ወጥቶ በባህር በር ጉዳይ የበኩሉን አስተዋፅዖ ሊያደርግ እንደሚገባ ሚኒስትሩ መናገራቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- FBC(Fana Broadcasting Corporate S.C.)
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.