Fana: At a Speed of Life!

በንፋስ ስልክ ቀለም ፋብሪካ ላይ ተከስቶ የነበረው የእሳት አደጋ በቁጥጥር ስር ዋለ

አዲስ አበባ፣ ጥር 6፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 በንፋስ ስልክ ቀለም ፋብሪካ ላይ ተከስቶ የነበረው የእሳት አደጋ በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡

የአዲስ አበባ የእሳትና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን እንዳስታወቀው÷ዛሬ ከቀኑ 8 ሰዓት አካባቢ በንፋስ ስልክ ቀለም ፋብሪካ ላይ የተከሰተውን የእሳት አደጋ በተደረገ ርብርብ ሙሉ ለሙሉ መቆጣጠር ተችሏል።

የአደጋው መንስኤ እና ሌሎች መረጃዎች እየተጣሩ መሆኑንም ኮሚሽኑ አመላክቷል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.