በጉብኝታቸውም በተመለከቱት ነገር እጅግ እንደተገረሙ መናገራቸውን የአዲስ አበባ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡
በዓድዋ ጦርነት ኢትዮጵያውያን የነጭ ወረራን ለመከላከል በአንድነት ቆመው ያደረጉት ተጋድሎ ለጥቁር ሕዝቦች የመብት ትግል ፋና ወጊ እንደነበርም አውስተዋል፡፡
ይህ ድል መላውን ጥቁር ሕዝብ የሚያኮራ ታሪክ ሲሆን÷ የጦርነቱን ታሪክና ጀግንነት እዚህ በዓድዋ ድል መታሰቢያ በአንድ ማዕከል ተዘጋጅቶ መመልከት መቻል ትልቅ እድል መሆኑንም ገልፀዋል።
የዓድዋ ድል ከኢትዮጵያውያን አልፎ የመላው ጥቁር ሕዝብ ልብ ውስጥ የታተመ የጋራ አኩሪ ድላችን ነው ሲሉም ገልጸዋል፡፡