የሐረሪ ክልል ሕዝብ በ #ጽዱኢትዮጵያ ዲጂታል ቴሌቶ ላይ በንቃት እንዲሳተፍ ጥሪ ቀረበ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 4፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሐረሪ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ኦርዲን በድሪ የክልሉ ሕዝብ በ #ጽዱኢትዮጵያ ዲጂታል ቴሌቶን ላይ በንቃት እንዲሳተፍ ጥሪ አቀረቡ፡፡
ለጽዱ ኢትዮጵያ በአንድ ጀምበር 50 ሚሊየን ብር ለማሰባሰብ ያለመ የዲጂታል ቴሌቶን እየተካሄደ ነው፡፡
ይህን አስመልክተው አቶ ኦርዲን ባስተላለፉት መልዕክት÷ የንቅናቄው ንጹህ አካባቢን በመፍጠር ለትውልድ ለማስተላለፍ ያለመ በመሆኑ የክልሉ ሕዝብ የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ ለዓላማው መሳካት አስተዋፅኦ እንዲያበረክት ጥሪ አቅርበዋል፡፡