ኢትዮጵያውያን ታዳጊ ህፃናት የአለም አቀፉ የሮቦ ፌስት ውድድር አሸናፊ ሆኑ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 4፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያውያን ታዳጊ ህፃናት በአሜሪካ በተካሄደው የአለም አቀፍ የሮቦ ፌስት ውድድር አሸናፊ ሆነዋል፡፡
ኢትዮጵያውያኑ ሶስት ሽልማቶችን የግላቸው ያደረጉ ሲሆን÷ የመጀመሪያው ከ 10 አመት በታች በተወዳደሩበት ሮቦ ፓሬድ የውድድር ዘርፍ ነው፡፡
ሁለተኛው ደግሞ በሲንየር ኤግዚቢሽን ከ 14 እስከ 16 አመት ስፔሻል አዋርድ ሽልማትን ማግኘት ችለዋል፡፡
በጁንየር እግዚቢሽን ዘርፍ ደግሞ በአለም አቀፍ ዉድድር የሶስተኝነትን ደረጃን ይዘው ያጠናቀቁ ሲሆን÷በተጨማሪም ከየውድድሩ ከ 1 እስከ 3 ለወጡ ተወዳዳሪዎች የሜዳሊያ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
አሜሪካ በሚገኘው የሚችጋን ላውረንስ ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በተካሄደው ውድድር 23 ታዳጊ ኢትዮጵያውያን ሀገራቸውን ወክለው በተለያዩ ዘርፎች ለውድድር መቅረባቸው የሚታወስ ነው፡፡