በንግድ ነፃ ቀጠናዎች አተገባበር ዙሪያ ውይይት ተካሄደ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 18፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ)የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር)በንግድ ነፃ ቀጠናዎች አተገባበር ዙሪያ ውይይት አድርገዋል፡፡
በዛንዚባር 14ኛው የአፍሪካ ንግድ ሚኒስትሮች የምክክር መድረክ እየተካሄደ ነው፡፡
በመድረኩ እየተሳተፉ የሚገኙት የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ከመድረኩ በተጓዳኝ ከአለም ነፃ ቀጠና ዋና ስራ አስፈፃሚ ሳሚር ሃሙሮኒ( ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል፡፡
በውይይታቸውም÷ በንግድ ነፃ ቀጠናዎች አተገባበር ዙሪያ ጠቃሚ ምክክር ማካሄዳቸውን በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው አስፍረዋል፡፡