Fana: At a Speed of Life!

አቶ ደስታ ሌዳሞ የዘንድሮውን ክልል አቀፍ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር አስጀመሩ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሲዳማ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ደስታ ሌዳሞ የዘንድሮውን ክልል አቀፍ የአረንጓዴ ዐሻራ የችግኝ ተከላ መርሐ- ግብር በሐዋሳ ዙሪያ ወረዳ ኡምቡሌ ዋጮ ቀበሌ በይፋ አስጀመሩ።

የዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ መርሐ-ግብር የሚከናወነው “የምትተክል ሀገር የሚያጸና ትውልድ” በሚል መሪ ሐሳብ ነው፡፡

በክልሉ በዘንድሮ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ለምግብነትና ለእንስሳት መኖነት የሚያገለግሉ ተክሎችን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች እንደሚተከሉ መገለጹን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

የችግኝ ተከላው ከ29 ሺህ ሄክታር በሚልቅ መሬት ላይ እንደሚካሄድም ነው የተመላከተው፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.