Fana: At a Speed of Life!

የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በዓል ለሀገር ገፅታ ግንባታ የላቀ ሚና አለው- አፈ-ጉባዔ አገኘሁ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 22፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በዓል ለሀገር ገፅታ ግንባታ የላቀ ሚና አለው ሲሉ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር አስገነዘቡ፡፡

“ሀገራዊ መግባባት ለኅብረ-ብሔራዊ አንድነት” በሚል መሪ ሐሳብ 19ኛው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ በአምቦ ዩኒቨርሲቲ ተከብሯል፡፡

አፈ-ጉባዔ አገኘሁ በአከባበሩ ላይ ባደረጉት ንግግር÷ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን መከበር ለሀገር ገፅታ ግንባታ የላቀ ሚና አለው ብለዋል።

በዓሉ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች የእርስ በርስ ትውውቅና የባህል ልውውጥ መድረክ መሆን መቻሉንም ተናግረዋል፡፡

ከዚህ ባለፈም የክልሎች መሠረተ-ልማትና ኢንቨስትመንት እንዲነቃቃ ብሎም ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ከዳር እንዲደርስ ትልቅ ሚና ተጫውቷል ማታቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

ሰላሟ የፀናና የበለፀገች ሀገርን ለመፍጠር ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓቱን እንዲጠብቁም ጥሪ አቅርበዋል።

19ኛው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች በዓል በሀገር አቀፍ ደረጃ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አርባ ምንጭ ከተማ ሕዳር 29 ቀን 2017 ዓ.ም ይከበራል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.