አየር መንገዱ 3ኛውን A350-1000 አውሮፕላን ተቀበለ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 24፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሦስተኛውን A350-1000 አውሮፕላን ከፈረንጆቹ 2025 ጋር አብሮ መቀበሉን ገልጿል፡፡
በዚህም አየር መንገዱ እንዳለው ፥ ምቹና ዘመናዊ አውሮፕላኖችን ስራ ላይ በማዋል ለደንበኞቻችን ምርጥ አገልግሎት ከመስጠት በተጨማሪ በአቪዬሽን መስኩ በአፍሪካ ስኬታማ የሆንበትን መሪነት እና በዓለም ደረጃ ያለንን ተወዳዳሪነት አጠናክረን እናስቀጥላለን።