ጋምቤላ የከተራ በዓልን እያከበረች ነው
አዲስ አበባ፣ ጥር 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የከተራ በዓል በጋምቤላ ከተማ በተለያዩ ሃይማኖታዊ ክዋኔዎች እየተከበረ ይገኛል።
በአከባበሩ ላይ ከተለያዩ አድባራት የተወጣጡ ታቦታት ከመንበረ ክብራቸው በመውጣት ወደ ባሕረ ጥምቀቱ እያመሩ ነው፡፡
በነገው ዕለት ደግሞ የጥምቀት በዓል በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስርዓቶች እንደሚከበር ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።