Fana: At a Speed of Life!

ከፍተኛ የመንግሥት ሥራ ኃላፊዎች በባሕር ዳር የልማት ሥራዎችን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 18፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በባሕር ዳር ከተማ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል፡፡

በጉብኝቱ የገቢዎች ሚኒስትር ዓይናለም ንጉሤ፣ በም/ርዕሰ መሥተዳድር ማዕረግ የከተማ ዘርፍ አሥተባባሪ እና የከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አሕመዲን መሐመድ (ዶ/ር) እና የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታን ጨምሮ የተለያዩ የመንግሥት ሥራ ሃላፊዎች ተሳትፈዋል።

የሥራ ኃላፊዎቹ የባሕር ዳር ከተማን የኮሪደር ልማት እና ሌሎች የልማት ሥራዎችን ተዘዋውረው መመልከታቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.