Fana: At a Speed of Life!

ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ከ1 ሺህ 800 በላይ ተማሪዎችን አስመረቀ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 30፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያና 2ኛ ዲግሪ ያስተማራቸውን 1 ሺህ 811 ተማሪዎችን በዛሬው ዕለት አስመርቋል።

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት አስማረ መለሰ (ዶ/ር) በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ወቅት እንዳሉት÷ዩኒቨርሲቲው ሀገር በቀል እውቀትን በመጠቀም በተለያዩ ዘርፎች የልሕቀት ማዕከል ለመሆን እየሰራ ነው፡፡

ለተመራቂ ተማሪዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ያስተላለፉት ፕሬዚዳንቱ ÷ ተመራቂዎች የቀሰሙትን ዕውቀትና ያካበቱትን ክህሎት ተጠቅመው ሀገራዊ ድርሻቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል።

ዩኒቨርሲቲው ለ17ኛ ጊዜ ካስመረቃቸው ተማሪዎች ውስጥ 46ቱ በ2ኛ ዲግሪ የተመረቁ ሲሆኑ÷ከአጠቃላይ ተመራቂዎች 527 የሚሆኑት ደግሞ ሴቶች መሆናቸው ተመላክቷል።

በግርማ ነሲቡ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.