ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ከ1 ሺህ 800 በላይ ተማሪዎችን አስመረቀ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 30፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያና 2ኛ ዲግሪ ያስተማራቸውን 1 ሺህ 811 ተማሪዎችን በዛሬው ዕለት አስመርቋል።
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት አስማረ መለሰ (ዶ/ር) በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ወቅት እንዳሉት÷ዩኒቨርሲቲው ሀገር በቀል እውቀትን በመጠቀም በተለያዩ ዘርፎች የልሕቀት ማዕከል ለመሆን እየሰራ ነው፡፡
ለተመራቂ ተማሪዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ያስተላለፉት ፕሬዚዳንቱ ÷ ተመራቂዎች የቀሰሙትን ዕውቀትና ያካበቱትን ክህሎት ተጠቅመው ሀገራዊ ድርሻቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል።
ዩኒቨርሲቲው ለ17ኛ ጊዜ ካስመረቃቸው ተማሪዎች ውስጥ 46ቱ በ2ኛ ዲግሪ የተመረቁ ሲሆኑ÷ከአጠቃላይ ተመራቂዎች 527 የሚሆኑት ደግሞ ሴቶች መሆናቸው ተመላክቷል።
በግርማ ነሲቡ