Fana: At a Speed of Life!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኢንዱስትሪ ዘርፍን በተመለከተ የሰጡት ምላሽና ማብራሪያ:-

👉 በኢንዱስትሪው ዘርፍ የነበረውን የውጭ ምንዛሬ አቅርቦት ችግር ለመቅረፍ መንግስት ጣልቃ በመግባት የኢኮኖሚ መሻሻያ አድርጓል፤ በዚህም ተጨባጭ ውጤት ተገኝቷል፣

👉 የሀይል አቅርቦት ችግርን ለመቅረፍ በተከናወኑ ተግባራት በዘርፍ ኢነርጂ 100 ፐርሰንት ተደራሽ ማድረግ ተችሏል፣ ከአምናው ጋር ሲነፃፀር በኢንዱስትሪው ዘርፍ 50 በመቶ የሀይል አቅርቦት ጭማሪ ተደርጓል፣

👉 ከግብዓት ጋር እንዲሁም ከኢንዱስትሪ መሬት አቅርቦት ጋር በተያያዘ መንግስት በርካታ ስራዎችን አከናውኗል፣

👉 ኢትዮጵያ 100 በመቶ የብረት ምርት በሀገር ውስጥ ማምረት ጀምራለች፤ በቀጣይም የብረት ምርት ግብዓቶችን ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ለማድረግ እየተሰራ ነው፣

👉  የሲሚንቶ አቅርቦት ችግርን ለመቅረፍ በተከናወኑ ተግባራት ፋብሪካዎችን ማስፋፋት ተችሏል፤ በዚህም ከሀገር ውስጥ ፍጆታ አልፎ ወደ ውጭ ሀገር ለመላክ የሚያስችል ሲሚንቶ ማምረት ተችሏል፣

👉 በተጨማሪም በሴራሚክስ፣ ግራናይት፣ ማርብል፣ የቴክስታይል እና የምግብ ማቀነባበሪያ ምርቶችን የማምረት ስራዎች በስፋት እየተሰሩ ይገኛሉ፣

👉 በአጠቃላይ በበጀት ዓመቱ ፋብሪካዎች የማምረት አቅማቸው 61 በመቶ ደርሷል፣ 55 አዳዲስ ግዙፍ ፋብሪካዎች ወደ ስራ ገብተዋል፤ በዚህም በበጀት ዓመቱ መጨረሻ በኢንዱስትሪው ዘርፍ የታቀደውን ግብ ማሳካት የሚያስችል አቅም ተገንብቷል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.