Fana: At a Speed of Life!

የቲቢ በሽታን ለመከላከል በትኩረት እየተሠራ ነው- ጤና ሚኒስቴር

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ሁሉ አቀፍ የሕብረተሰብ ጤና ችግር የሆነውን የቲቢ በሽታ ለመከላከልና ለመግታት በትኩረት እየተሠራ መሆኑን የጤና ሚኒስትር ዴዔታ ደረጄ ዱጉማ (ዶ/ር) ገለፁ፡፡

19 ኛው ዓመታዊ የቲቢ ምርምር ጉባዔ እና የ2017 ዓ.ም የዓለም የቲቢ ቀን በአርባምንጭ እየተከበረ ነው፡፡

ሚኒስትር ዴዔታው በዚሁ ወቅት፤ ‎የሕብረተሰቡን ግንዛቤ በማሳደግና በሽታውን ለመግታት ከ100 በላይ ጥናትና ምርምሮች መከናወናቸውን ጠቁመዋል፡፡

ከነዚህ ጥናትና ምርምሮች መካከልም 20ዎቹ ተመርጠው በመድረኩ እየቀረቡ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ አመላክቷል፡፡

‎ከዚህ ቀደም የቲቢ በሽታን መርምሮ ለማሳወቅ ሦስት ቀናት እንደሚፈጅ አውስተው፤ አሁን ላይ በደቂቃዎች ማሳወቅ የሚችል 1 ሺህ ማሽን ለ140 በላይ ተቋማት ተደራሽ መደረጉን ተናግረዋል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.