Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያ ቡና እና ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 21፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ32ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ኢትዮጵያ ቡና እና ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ በአቻ ውጤት ተለያተዋል፡፡

ቀን 9 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም የተደረገው ጨዋታ ግብ አልተቆጠረበትም።

ቀደም ሲል ዛሬ ረፋድ 3:30 ላይ በተካሄደ ጨዋታ አዳማ ከተማ ሀድያ ሆሳዕናን በረከት ወ/ዮሐንስ (በራስ ላይ) ባስቆጠራት ግብ 1 ለ 0 ማሸነፉ ይታወሳል።

የ32ኛ ሳምንት የጨዋታ መርሐ ግብር ምሽት 12 ሰዓት ላይ ቀጥሎ ሲካሄድ ወላይታ ድቻ ከኢትዮ ኤሌክትሪክ ይገናኛሉ።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.