Fana: At a Speed of Life!

ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን የሙዚቃ መሳሪያዎችን ድጋፍ አደረገ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 2፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን የተለያዩ የሙዚቃ መሳሪያዎችን ለጉለሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ባህል፣ ኪነጥበብ እና ቱሪዝም ፅህፈት ቤት ድጋፍ አድርጓል።

በፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን የዋና ስራ አስፈፃሚ ፅህፈት ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ አዶኒያስ ወልደ አረጋይ በርክክቡ ወቅት እንዳሉት፤ ትውልድን ለመገንባት እና ትውልድ እንዲገለገልበት በማሰብ ድጋፉ ተደርጓል።

ፋና ሀገራዊ ተቋም እንደመሆኑ የተለያዩ ለሀገር የሚጠቅሙ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ አስታውሰው የዛሬው ድጋፍም የዚህ ተልዕኮ አንድ አካል ነው ብለዋል።

እንዲሁም ፋና በተሰማራበት የሚዲያ ዘርፍ የተለያዩ ለትውልድ የሚጠቅሙ ስራዎችን በመስራት እንደሚገኝ እና እንደዚህ ያሉ ድጋፎችን ማድረጉንም እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

የጉለሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ወልዴ ወገሴ በበኩላቸው ከፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ስለተደረገላቸው የሙዚቃ መሳሪያ ድጋፍ አመሰግነዋል።

ኮርፖሬሽኑ በዛሬው ዕለት ካበረከታቸው የሙዚቃ መሳሪያዎች መካከል ፒያኖ፣ ጊታር፣ ክራር እና ስፒከር የመሳሰሉ የሙዚቃ መሳሪያዎች እንደሚገኙበት ተጠቅሷል።

በወንድማገኝ ጸጋዬ

 

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

 

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

Facebook WMCC

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.