ለጣና ነሽ ፪ ጀልባ በአዳማ ከተማ አቀባበል ተደረገ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በጣና ሐይቅ የመዝናኛና የትራንስፖርት አገልግሎት ለመስጠት ወደ ሀገር የገባችው ጣና ነሽ ፪ ጀልባ አዳማ ከተማ ደርሳለች።
ጀልባዋ በዛሬው ዕለት አዳማ ከተማ ስትደርስ የከተማዋ ነዋሪዎች ወደ አደባባይ በመውጣት አቀባበል አድርገዋል።
እንዲሁም የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ አቶ ኃይሉ ጀልዴን ጨምሮ የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ የሥራ ኃላፊዎች በአቀባበል ሥነ ሥርዓቱ ላይ ተገኝተዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጀልባዋን ለማሳለፍ በመንገድ ላይ ያሉ የኤሌክትሪክ ገመዶችን በማንሳት እንዲሁም የሚቋረጡ የኤሌክትሪክ አገልግሎቶችን በፍጥነት በመመለስ ርብርብ እያደረጉ ይገኛሉ።
በተጨማሪም የከተማው አስተዳደር የትራፊክ መብራቶችን በማንሳት ጭምር ጀልባዋ በምታልፍባቸው መንገዶች አስፈላጊውን ትብብር በማድረግ ላይ ነው።
ጣና ነሽ ፪ ዘመናዊ የህዝብ ትራንስፖርት ጀልባ 38 ሜትር ርዝመት ያላት ሲሆን፥ በአንድ ግዜ 188 ሰዎችን የመጫን አቅም እንዳላት የባህር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ መረጃ ያመለክታል።
በኃይለማርያም ተገኝ
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!