ሰላምና መቻቻል እንዲጎለብት የኃይማኖት ተቋማት የጀመሩትን አስተምህሮ እንዲያጠናክሩ ተጠየቀ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) “ሃይማኖቶች ለሰላም፣ ለመከባበርና ለአብሮነት” በሚል መሪ ሐሳብ 3ኛው ሀገር አቀፍ የሰላም ጉባኤ በባሕር ዳር ከተማ እየተካሄደ ይገኛል፡፡
የሰላም ጉባኤው የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ከአማራ ክልል የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ነው።
በጉባኤው መክፈቻ ላይ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አረጋ ከበደ ባስተላለፉት መልዕክት÷ የሃይማኖት ተቋማት የሀገር ሰላም፣ የህዝብ አንድነት እና ልማት እንዲጠናከር የላቀ ሚና እንዳላቸው ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ የግጭት መንስኤዎችን በመፍታት ዘላቂ ሰላም እና ልማትን እውን ለማድረግ በውይይት መግባባት ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።
የኃይማኖት ተቋማት የሰላም ጉባኤ በባህርዳር መካሄዱ ልዩ ትርጉም እንዳለው አንስተው÷ በክልሉ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ሁሉን አቀፍ ጥረት እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል።
ሰላምና መቻቻል እንዲጎለብት፣ ዘላቂና አስተማማኝ ሰላም እንዲሰፍን እንዲሁም የህዝብና የመንግስት ግንኙነት የሰመረ እንዲሆን የሃይማኖት ተቋማት የጀመሩትን አስተምህሮ አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል።
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ዋና ፀሐፊ ቀሲስ ታጋይ ታደለ በበኩላቸው÷ ለግጭት መንስኤ የሆኑ ጉዳዮችን በመነጋገርና በውይይት መፍታት የሁሉም ግደታ መሆኑን አንስተዋል።
በ3ኛ የሃይማኖት ተቋማት የሰላም ጉባኤም በሀገራችን እንዳንድ አካባቢዎች የታዩ ግጭቶችን በመነጋገርና በመመካከር ለመፍታት የሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ለመምከር መሆኑን ገልጸዋል።
በመድረኩ የክልሉ ከፍተኛ ሥራ ኃላፊዎች እና ከክልሉ ሁሉም አካባቢዎች በሃይማኖት ተቋማት የተወከሉ የሃይማኖት አባቶች ተገኝተዋል።
የሰላም ጉባኤው ከዛሬ ጀምሮ ለሁለት ቀናት የሚቆይ ሲሆን÷ ዘላቂ ሰላምን ለማጽናት የሚኖረው ሚና የላቀ ነው ተብሏል፡፡
በደሳለኝ ቢራራ
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!