ከ100 በላይ የኤምፖክስ ለይቶ ማቆያና ማከሚያ ማዕከላት ተዘጋጅተዋል
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በመላው ኢትዮጵያ ከ100 በላይ የኤምፖክስ ለይቶ ማቆያና ማከሚያ ማዕከላት ተዘጋጅተዋል አለ፡፡
በኢንስቲትዩቱ የኤምፖክስ ቅኝት አስተባባሪ ሚኪያስ አላዩ ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንደገለፁት፤ በሁሉም ክልሎችና በሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች በሽታውን መቆጣጠር የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ተሰርተዋል።
የለይቶ ማቆያና ማከሚያ ማዕከላትም ቀድመው ዝግጁ መደረጋቸው በሽታውን በቀላሉ ለመግታት ያስቸላል ነው ያሉት።
በተጨማሪም ፈጣን ምላሽ የሚሰጥ ቡድን በማቋቋም የኤምፖክስ በሽታ እንዳይስፋፋ ሰፊ የቅኝት ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡
ከበሽታው ጋር ለተያያዙ መረጃዎችና ጥቆማ ለማድረግ ደግሞ 8335 እና 952 ነፃ የስልክ መስመሮችን መጠቀም እንደሚቻል አቶ ሚኪያስ አላዩ አመላክተዋል፡፡
የኤምፖክስ በሽታ በኢትዮጵያ መገኘቱ ከተገለጸበት ጊዜ ጀምሮ እስከ ትናንትናው ዕለት ድረስ 24 ሰዎች በበሽታው መያዛቸው በላቦራቶሪ በተደረገ ምርመራ ተረጋግጧል።
በዙፋን ካሳሁን
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!