የአማራ ክልል የሽምግልና መማክርት ምስረታ ማብሰሪያ ገባኤ ተካሄደ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአማራ ክልል የሽምግልና መማክርት ምስረታ የማብሰሪያ ገባኤ በባሕር ዳር ከተማ ተካሄደ።
በጉባኤው በአማራ ክልል ከሚገኙ 22 ዞኖች የተመረጡ የሀገር ሽማግሌዎች የተካተቱበት ክልላዊ የሽምግልና መማክርት ተመስርቷል።
የሽማግሌዎች መማክርት መመስረት ሀገር በቀል የሽምግልና ሥርዓቶች ለዘላቂ ሰላም ግንባታ ያላቸውን ዋስትና መሰረት በማድረግ ባህላዊ የሰላም እሴቶችን ለማዳበር የሚኖረው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑ ተገልጿል።
የሽማግሌዎች መማክርት ጉባኤ ራሱን የቻለ መተዳደሪያ ደንብ ያለው ሆኖ በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የሚደገፍና በገለልተኝነት ለሀገር ሰላም የሚሠራ የባህል አደረጃጀት ነው።
በማብሰሪያ መርሐ ግብሩ ላይ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ፣ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና፣ ማኅበራዊ ጉዳዮች፣ ባህልና ስፖርት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወርቀሰሙ ማሞን ጨምሮ የአማራ ክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
በደሳለኝ ቢራራ
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!