Fana: At a Speed of Life!

በኢትዮጵያ ዲጂታል የገንዘብ ዝውውር 12 ነጥብ 5 ትሪሊየን ብር ደረሰ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 26፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ ዲጂታል የገንዘብ ዝውውር 12 ነጥብ 5 ትሪሊየን ብር ደርሷል አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው በሰጡት ማብራሪያ፥ የፋይናንስ ዘርፍ በዚህ ዓመት አዎንታዊና ጤናማ ዕድገት አስመዝግቧል ብለዋል።

ዲጂታል የገንዘብ ዝውውር 12 ነጥብ 5 ትሪሊየን ብር መድረሱን ገልጸው፥ ከጥሬ ገንዘብ ግብይቱም ከፍተኛ ብልጫ እንዳለው አንስተዋል፡፡

የሞባይን ገንዘብ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር 55 ሚሊየን መድረሱን ገልጸው፥ ለ11 ሚሊየን የጥቃቅንና አነስተኛ ተበዳሪዎች 24 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በዲጂታል ብድር አማካኝነት ተደራሽ ሆኗል፡፡

በአጠቃላይ በዓመቱ የታቀደው 8 ነጥብ 4 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት እንደሚሳካ በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ በማዕድን፣ በአገልግሎትና ሌሎችም ዘርፎች የተገኙ ውጤቶች አመላካች ናቸው ብለዋል።

በኃይለማርያም ተገኝ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.