Fana: At a Speed of Life!

ፕሬዚዳንት ታዬ የኮሞሮስ ነጻነት በዓል ላይ ለመታደም ሞሮኒ ኮሞሮስ ገቡ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በ50ኛው የኮሞሮስ ነጻነት በዓል ላይ ለመሳተፍ ሞሮኒ ኮሞሮስ ገብተዋል።

ፕሬዚዳንቱ ሞሮኒ ልዑል ሰይድ ኢብራሂም ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የሀገሪቱ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ኮሞሮስ ከፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ነጻ የወጣችው ሰኔ 29 ቀን 1967 ዓ.ም ሲሆን÷ በነገው ዕለት የምታከብረው 50ኛውን የነጻነት በዓሏን ነው።

በነጻነት በዓሉ ለመታደም ፕሬዚዳንት ታዬን ጨምሮ የሴኔጋል፣ ታንዛኒያ፣ ሞሮኮ፣ ማዳጋስካር፣ ሞሪታንያ እና ሌሎች የአፍሪካ መሪዎች ኮሞሮስ መግባታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.