Fana: At a Speed of Life!

በግብርና መስክ የተሰማሩ ባለሃብቶች አርሶ አደሩን በቴክኖሎጂ መደገፍ አለባቸው – ወ/ሮ ዓለሚቱ ኡሞድ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ‎በጋምቤላ ክልል የግብርና ልማትን በማዘመን የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት የባለሃብቶች ተሳትፎ ሊጠናከር ይገባል አሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ወ/ሮ ዓለሚቱ ኡሞድ።

ርዕሰ መስተዳድሯ በጋምቤላና አበቦ ወረዳዎች ከዘርፍ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን በባለሃብቶች እየለማ የሚገኝን ማሣ ዛሬ በተመለከቱበት ወቅት እንዳሉት፤ ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት ኢንቨስትመንት የላቀ ድርሻ አለው።

‎ባለሀብቶች ባሉት ሰፊ የኢንቨስትመንት አማራጮች በመሰማራት ለክልሉ ልማትና እድገት ተሳትፏቸውን ሊያጠናክሩ እንደሚገባ ተናግረዋል።

በተለይም የግብርናውን ልማት በማዘመን የምግብ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ ለተጀመረው ጥረት በግብርና መስክ የተሰማሩ ባለሃብቶች አርሶ አደሩን በቴክኖሎጂ በመደገፍ ረገድ የበኩላቸውን ሚና ሊወጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

ባለሃብቶች በግብርና ላይ ተሰማርተው ተጠቃሚ መሆናቸውን የገለጹት ርዕሰ መስተዳድሯ÷ ሌሎች ባለሃብቶችም ወደ ክልሉ በመምጣት በተመሳሳይ ልማት እንዲሰማሩ ጥሪ አቅርበዋል።

የክልሉ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሎው ኡቡፕ (ዶ/ር) በበኩላቸው÷ በክልሉ አስተማማኝ ሰላም በመፈጠሩ በተለያዩ  የኢንቨስትመንት አማራጮች ለመሰማራት ወደ አካባቢው የሚመጡ ባለሃብቶች ፍሰት ጨምሯል ብለዋል።

‎በተለይም በግብርና መስክ ፍቃድ የወሰዱ ባለሃብቶች ወደ ልማት በመግባት ውጤታማ ስራዎችን እያከናወኑ እንደሆነ ገልጸው፤ ለባለሃብቶቹ አስፈለጊው ድጋፍ እየተደረገ ይገኛል ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

 

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.