Fana: At a Speed of Life!

የሠሜን ምዕራብ ዕዝ አባላት ችግኝ በመትከል አረንጓዴ አሻራቸውን አኖሩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በሀገር መከላከያ ሠራዊት የሠሜን ምዕራብ ዕዝ አባላት በጎንደር ከተማ ችግኝ በመትከል አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል።

ችግኝ ተከላው ‘በመትከል ማንሰራራት’ በሚል መሪ ሀሳብ ዘንድሮ ለሰባተኛ ጊዜ እየተካሄደ ያለው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር አካል መሆኑ ተገልጿል።

በችግኝ ተከላው ላይ የተገኙት የዕዙ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንደተናገሩት፤ ሠራዊቱ የሀገሩን ሠላም እና ሉዓላዊነት ከመጠበቅ ባሻገር በልማት አጀንዳዎች ላይ በንቃት እየተሳተፈ ነው።

የችግኝ ተከላው ሠራዊቱ ከህዝቡ ጋር ያለውን ትስስር ይበልጥ የሚያጠናክርበት መሆኑንም ገልጸው፤ ሀገርን ለማጽናት ከሚደረገው ትግል ጎን ሁሉም ክፍለጦሮች በአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ተሳትፎ ያደርጋሉ ነው ያሉት።

በዕለቱ የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር የዕዙ ከፍተኛ አመራሮች እና የ502ኛ ኮር የሠራዊት አባላት ተሳታፊ ሆነዋል።

በበላይነህ ዘለዓለም

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.