Fana: At a Speed of Life!

በተኪ ምርቶች ከ4 ቢሊየን ዶላር በላይ ወጪ ድኗል

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 21፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የተመረቱ ተኪ ምርቶች 4 ነጥብ 3 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላርን ማዳን ችለዋል አለ።

በማኒስቴሩ የተኪ ምርቶች ተወዳዳሪነት ሥራ አስፈፃሚ መሣይነህ ውብሸት ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንዳሉት፤ በአሁኑ ወቅት ተኪ ምርቶች ለሀገር ኢኮኖሚ ወሳኝ ድርሻ እየተወጡ ነው።

ለኮሪደር ልማቱ የሚያገለግሉ ስማርት ፖሎችን፣ ትራንስፎርመሮችን፣ የተለያዩ የኤሌክትሪክ ገመዶችን እና መሠል ግብዓቶችን በተኪ ምርቶች ማሟላት እየተቻለ ነው ብለዋል።

ለተኪ ምርቶች የተሰጠው ትኩረት የኢንዱስትሪዎች የእርስ በርስ ትስስር እንዲጠናከር ምቹ ሁኔታ መፍጠሩንም ተናግረዋል።

በተያዘው በጀት ዓመት 5 ነጥብ 7 ቢሊየን ዶላር በተኪ ምርቶች አማካኝነት ለማዳን ዕቅድ መያዙን አቶ መሣይነህ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ባመጣው ውጤት የተኪ ምርቶች የሀገር ውስጥ የገበያ ድርሻ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱንም አንስተዋል።

በሰለሞን ይታየው

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.