Fana: At a Speed of Life!

በሲዳማ ክልል በአንድ ጀንበር 8 ሚሊየን ችግኝ ይተከላል

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 23፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የሲዳማ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ በክልሉ በአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር 8 ሚሊየን ችግኝ ለመትከል ዝግጅት ተደርጓል አለ ።

በቢሮው የተፈጥሮ ሀብትና አነስተኛ መስኖ ልማት ዳይሬክተር አቶ በረከት አሰፋ ለፋና ዲጂታል እንዳሉት፥ በክልሉ የአንድ ጀንበር የችግኝ ተከላ ላይ ከ2 ነጥብ 5 ሚሊየን በላይ ሰዎች እንደሚሳተፉ ይጠበቃል።

ለችግኝ ተከላው 235 ቦታዎች መለየታቸውን፣ የጉድጓድ ዝግጅት መደረጉንና የችግኝ ስርጭት ስራዎች መከናወናቸውን ጠቅሰው፥ ከ2 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በችግኝ ይሸፈናል ብለዋል።

በክልሉ በነገው ዕለት በአንድ ጀንበር ከሚተከሉት 8 ሚሊየን ችግኞች ውስጥ 60 በመቶ የሚሆነው ለአካባቢ ጥበቃ፣ ቀሪው ደግሞ ለምግብነት እና ለደን ሽፋን የሚውሉ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በሲዳማ ክልል በዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር 307 ነጥብ 7 ሚሊየን ችግኝ ለመትከል ታቅዶ በእስካሁን 299 ነጥብ 7 ሚሊየን ችግኞች ተተክለዋል ነው ያሉት።

በክልሉ በነገው ዕለት የሚከናወነውን የአንድ ጀንበር የችግኝ ተከላ ሙሉ በሙሉ ለማሳካት ህብረተሰቡ በነቂስ እንዲሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል።

በኃይለማርያም ተገኝ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.