Fana: At a Speed of Life!

በኦሮሚያ ክልል ከ7 ነጥብ 5 ሚሊየን በላይ ህፃናትን በቀዳማይ ልጅነት ፕሮግራም ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ ነው

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 29፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኦሮሚያ ክልል በተያዘው በጀት ዓመት ከ7 ነጥብ 5 ሚሊየን በላይ ህፃናትን በቀዳማይ ልጅነት ፕሮግራም ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ ነው።

የክልሉ ቀዳማይ ልጅነት ፕሮግራም አስተባባሪ ታምሩ ታደሰ የቀዳማይ ልጅነት ፕሮግራም በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ ይተገበር እንደነበር ገልጸው÷ የኦሮሚያ ክልል ኢኒሼቲቩን በመውሰድ በሁሉም አካባቢዎች እንዲጀመር መወሰኑን ተናግረዋል።

በዚህም ክልሉ በ415 ወረዳዎች 17 ሺህ 200 የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በመገንባት ፕሮግራሙ ስራ ላይ እንዲውል መደረጉንና በ750 ጤና ጣቢያዎች እና በተወሰኑ ሆስፒታሎች ላይ ስራው መጀመሩን ጠቁመዋል።

የጤና፣ የትምህርት እንዲሁም የሴቶችና ህፃናት ጉዳዮች ቢሮ ጉዳዩን በባለቤትነት እየሰሩ መሆናቸውንም አቶ ታምሩ ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ገልጸዋል።

ፕሮግራሙ ከተጀመረ አንድ ዓመት አካባቢ እንደሆነው እና የስትራቴጂክ ፕላን መዘጋጀቱን እንዲሁም የስትሪንግ ኮሚቴ መቋቋሙን አንስተው÷ ክልሉ ካለው ስፋት እና ከበጀት አንፃር ሰፊ ስራ እንደሚጠበቅ አስረድተዋል።

በተያዘው በጀት ዓመት ዕድሜያቸው ከ6 ዓመት በታች የሆኑ 7 ነጥብ 5 ሚሊየን ህፃናትን እና በርካታ የሚያጠቡ እና ነፍሰ ጡር እናቶችን ተደራሽ ለማድረግ መታቀዱን ጠቅሰው÷ እስካሁን ለ4 ነጥብ 5 ሚሊየን እናቶች የአልሚ ምግብ ድጋፍ መደረጉን አመልክተዋል።

በተጨማሪም በ33 ከተሞች የቤት ለቤት የምክር አገልግሎት ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ እንደሆነና 11 ሚሊየን ለሚጠጉ ህፃናት እና ወላጆች የምክር አገልግሎት መሰጠቱን ጠቁመዋል።

በመሳፍንት እያዩ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.