Fana: At a Speed of Life!

ዘላቂ ሰላም የሚረጋገጠው ሁሉም ባለድርሻዎች በጋራ ሲሰሩ ነው – አቶ መሀመድ እድሪስ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 3፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ዘላቂ ሰላም የሚረጋገጠው የጸጥታ አካላትን ጨምሮ ሁሉም ባለድርሻዎች በጋራ ሲሰሩ ነው አሉ የሰላም ሚኒስትር መሀመድ እድሪስ፡፡

‎የሰላም ሚኒስቴር በተለያዩ አካባቢዎች የሚከሰቱ ችግሮች ወደ ግጭት ሳይሻገሩ ለማስቀረት ያለመ የውይይት መድረክ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ጨምሮ የተለያዩ ባለድርሻዎች በተገኙበት በአዳማ ከተማ እያካሄደ ይገኛል፡፡

‎አቶ መሀመድ እድሪስ በመድረኩ እንዳሉት÷ የኢትዮጵያን ብልፅግና እውን ለማድረግ ሰላምን ማፅናት ያስፈልጋል ብለዋል።

የተገኘውን አንጻራዊ ሰላም ማጽናት የሁሉም ዜጋ ሀላፊነት እንደሆነ ገልጸዋል።

‎ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ለማድረግ ጥረቶች እየተደረጉ እንደሆነ ገልጸው÷ ዘላቂ ሰላም የሚረጋገጠው የጸጥታ አካላትን ጨምሮ ባለድርሻዎች በጋራ ሲሰሩ ነው ብለዋል።

ዘላቂ ሰላም ሲረጋገጥ የተጀመረው ልማት ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስገንዝበዋል።

‎መድረኩ በሀገራዊ የሰላም ግንባታ የግጭት አፈታትና ሀገር ግንባታ ዙሪያ ላይ የተሟላ ግንዛቤ በመያዝ ልማትን ለማጎልበት የሚያስችል ግልጽነትና ዝግጁነት ያለው አመራር ለመገንባት ያለመ መሆኑ ተመላክቷል፡፡

‌‎በሀይማኖት ወንድይራድ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.