ፕሬዚዳንት ትራምፕ ከሩሲያው አቻቸው ጋር ለመምከር ወደ አላስካ አቀኑ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት ዙሪያ ከከሩሲያ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ለመምከር ወደ አላስካ ግዛት አቅንተዋል፡፡
ሁለቱ መሪዎች ዛሬ ምሽት ፊት ለፊት በመገናኘት እንደሚመክሩ ይጠበቃል፡፡
ከውይይቱ አስቀድሞ አላስካ የገቡት የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ በሰጡት መግለጫ፤ ሀገራቸው አሜሪካ በቀላሉ የምትረዳውን ግልጽ የድርድር ሃሳብ ይዛ ትቀርባለች ብለዋል፡፡
የፕሬዚዳንት ትራምፕ ልዩ መልዕክተኛ ስቲቭ ዊትኮፍ ሞስኮ በነበሩበት ወቅት ተስፋ ሰጭ ውይይት አድርገናል ያሉት ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ፤ በሁለቱ ፕሬዚዳንቶች መካከል የሚደረገው ውይይት ሁሉንም ወገን አሸናፊ እንደሚያደርግ እምነታቸውን ገልጸዋል።
በዛሬ ምሽቱ የሁለቱ ሀገራት ፕሬዚዳንቶች ውይይት የሀገራቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች እና ሌሎች ዲፕሎማቶች ይገኛሉ መባሉን ሲኤንኤን እና አር ቲ ዘግበዋል፡፡
በሚኪያስ አየለ
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!