Fana: At a Speed of Life!

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለብሔራዊ ጥቅም…

‎አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ህግ የተቀመጡ መብቶቿንና ብሔራዊ ጥቅሟን በዘላቂነት እንድታስጠብቅ መሰረት የጣለ ነው አሉ ምሁራን።

‎ብዙ ፈተናዎችን ያለፈው የሕዳሴ ግድቡ ኢትዮጵያ ለዘመናት የተነፈገችውን በዓባይ ወንዝ የመጠቀም መብትን ያረጋገጠ ብቻ ሳይሆን በሌሎች የተፈጥሮ ሀብቶቿ ብሔራዊ ጥቅሞቿን በዘላቂነት ማስጠበቅ የምትችልበትን መሠረት የጣለ መሆኑንም ተናግረዋል።

‎በጅማ ዩኒቨርሲቲ የዓለም አቀፍ ፖለቲካ ኢኮኖሚ መምህር ፍቃዱ ቶሎሳ (ዶ/ር) የግድቡ መጠናቀቅ ብዙ ለውጦችን ይዞ ይመጣል ብለዋል።

በተፈጥሮ ሀብት አጠቃቀም አዲስ ስምምነቶች እንዲፈጠሩ የሚያደርግ መሆኑን ጠቁመዋል።

ግድቡ የቅኝ ግዛት ስምምነቶች ዋጋ እንደሌላቸው አረጋግጧል ያሉት ፍቃዱ ቶሎሳ (ዶ/ር)÷ ከአሁን በኋላ የተፈጥሮ ሀብት አጠቃቀምን በተመለከተ የጋራ ትብብርን መሰረት ያደረጉ አዳዲስ ስምምነቶች ይፈጠራሉ ነው ያሉት።

‎በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የዓለም አቀፍ ህግ መምህር እውነቱ ተስፋዬ በበኩላቸው÷ የግድቡ የምረቃ ዋዜማ ላይ መገኘት ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ህግ የተቀመጡ በተፈጥሮ ሀብት የመጠቀም መብቶቿን ያረጋገጠችበት መሆኑን አስረድተዋል።

‎ኢትዮጵያ በወንዞቿና ሌሎች የተፈጥሮ ሀብቶቿ ፍትሃዊ ተጠቃሚነት እንዲኖር ግድቡ በጎ ተጽዕኖ ማሳደሩን ገልጸው÷ ይህም ከአጎራባችና ሌሎች ሀገራት ጋር የተፈጥሮ ሀብትን በትብብር በመጠቀም የተሻለ ግንኙነት እንዲኖራት ያስችላል ብለዋል።
‌‎
‎በተስፋየ ምሬሳ

 

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

 

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.