ፕሬዚዳንት ታዬ በአርቲስት ደበበ እሸቱ ሕልፈት የተሰማቸውን ሃዘን ገለጹ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 11፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በአርቲስት ደበበ እሸቱ ሕልፈት የተሰማቸውን ሃዘን ገልጸዋል፡፡
ፕሬዚዳንቱ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት የሃዘን መግለጫ÷አንጋፉውና ተወዳጁ የኪነጥበብ ሰው ደበበ እሸቱ ከዚህ ዓለም በሞት በመለየቱ የተሰማኝን ጥልቅ ሐዘን እገልጻለሁ ብለዋል።